News News
Minimize Maximize
« Back

የከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ሚኒስቴርና የሶማሌ ክልላዊ መንግስት 8ኛው የኢትዮጵያ ከተሞች ፎረም ዙሪያ ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጡ

የአትዮጵያ ከተሞች ፎረም በኢ... የከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ሚኒስቴር አስተባባሪነት በየሁለት አመቱ ይካሄዳል ፡፡ ፎረሙ መካሄድ ከጀመረ  ዘጠኝ ዓመታትን ያስቆጠረ ሲሆን በዚህም ሰባት ከተሞች የአዘጋጅነት እድል አግኝተዋል፡፡

ዘንድሮ  ፎረም ለ8ተኛ ጊዜ በሶማሌ ክልላዊ መንግስት ዋና ከተማ ጅግጂጋ መደመር ለኢትዮጵያ ከተሞች ብልፅግናበሚል መሪ ቃል ከየካቲት 9 ቀን ጀምሮ እስከ የካቲት 14 ቀን 2011 . ለተከታታይ ሰባት ቀናት በደማቅ ሁኔታ የሚከበር ሲሆን  የፎረሙን ቅድመ ዝግጅት ስራዎች የደረሱበትን ደረጃ በተመለከተ ለህብረተሰቡ ግንዛቤ ለመስጠት በከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ እና የፎረሙ አብይ ኮሚቴ ሰብሳቢ አቶ ካሳሁን ጎፌ እንዲሁም የሶማሌ ክልላዊ መንግስት የከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ቢሮ ሃላፊ / አብድልፈታ ሼህ ቢህ በተገኙበት ጥር 15 ቀን 2011. ለሚዲያ አካላት ጋዜጣዊ መግለጫ ተሰጥቷል፡፡
  በጋዜጣዊ መግለጫው ሚኒስትር ዴኤታው እንደገለጹት የከተሞች ፎረም መካሄድ ከጀመረበት ጊዜ አንስቶ በከተሞች ከፍተኛ የሆነ መሰረታዊ ለውጥ መምጣቱን ጠቅሰው ዘንድሮ 8 ጊዜ በጅግጅጋ ከተማ የሚካሄደው የከተሞች ፎረም የቅድመ ዝግጅት ስራዎች በማጠናቀቅ ላይ እንደሚገኙ ተናግረዋል፡፡ እስካሁን ድረስም 109 ከተሞች እና ሁለት ድርጅቶች የተመዘገቡ ሲሆን ምዝገባው ጥር 25 ቀን 2011. የሚጠናቀቅ በመሆኑ ተሳታፊ የሚሆኑከተሞች ካሁኑ ምዝገባቸውን ማጠናቀቅ እንደሚገባቸው ተናግረዋል፡፡ አቶ ካሳሁን አክለውም በፎረሙ ለመካፈል የተመዘገቡ ከተሞች በቂ ዝግጅት ማድረግ እንዳለባቸው የገለጹት ሲሆን ከተሞች በፎረሙ ለመሳተፍ ወደ ጅግጅጋ በሚተላላፉበት ጊዜ አጎራባች የሆኑ ክልሎችና ከተሞች በኢትዮጵያዊነት እንግዳ አቀባበል እንዲያስተናግዷቸው ጥሪ አቅርበዋል፡፡

በሶማሌ ክልላዊ መንግስት የከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ቢሮ ሃላፊ / አብድልፈታ ሼህ ቢህ በበኩላቸው የቅድመ ዝግጅት ሥራዎች 95% በላይ መጠናቀቃቸውን ጠቅሰው የክልሉ ሰላም በጥሩ ሁኔታ ላይ እንደሚገኝ እና የሠላሙ ጠባቂ እራሱ ህብረተቡ በመሆኑ ከህብረተሰቡ እና ከሚመለከታቸው አካላት ጋር ከፍተኛ ውይይት ተደርጓል፡፡ ስለዚህ የከተማው ህብረሰብ የሚመጡ እንግዶችን ደህንነት ለመጠበቅ ግንባር ቀደም ተሳተፊ ይሆናሉ ብለዋል፡፡ አክለውም ጅግጅጋ ሶማሌ ክልልን ብቻ ሳይሆን ኢትዮጺያዊ  እንግዳ አቀባበልን በሚመጥን መልኩ እንግዶቹን ለመቀበል ኢትዮጺያን ወክላ ስለተዘጋጀች መጥታችሁ እንድትጎበኙን የሚል መልዕክት አስተላልፈዋል ፡፡

በፎረሙም 200 በላይ የሚሆኑ የኢትዮጵያና 10 በላይ የሚሆኑ የጎረቤት ሀገር እህት ከተሞች ተሳታፊ ይሆናሉ ተብሎ ይጠበቃል ፡፡