Prease release Prease release
Minimize Maximize

 በቀጣይ ዓርብ ነሐሴ 27/2008 . የአዲስ አበባ ከተማ ስራ አስኪያጅ /ቤት ሁሉም የመስሪያ ቤቱ ሰራተኞች፣የስራ ሂደት መሪዎችና አመራሮች በተገኙበት የበጀት ዓመቱን የእቅድ አፈፃፀም እንደሚገመግም አስታወቀ፡፡  

  የጽ/ቤት ኃላፊው አቶ ካሳ ወዳጅ እንዳሉት የግምገማው ዋና ዓላማ 2008 በጀት ዓመት እቅድ የስራ አፈፃፀም በጽ/ቤት ደረጃ በመገምገም በጥንካሬ ያሉ መልካም ስራዎች ተጠናክረው እንዲቀጥሉ እና በአፈፃፀም በኩል ውስንነት የተስተዋለባቸው የቀጣይ የእቅድ አካል ሆነው ትኩረት ተሰጥቶባቸው እንዲሰሩ ለማድረግ ተስቦ መሆኑን ገልፀዋል ፡፡

በሌላ በኩል የጽ/ቤት ኃላፊው  አክለው እንደገለፁት የግምገማ መድረኩ በጽ/ቤቱ ስር ያሉ የሁሉም የስራ ሂደቶች፣ደጋፊ የስራ ሂደቶችና የስራ ክፍሎችን  ሪፖርቶች በአንድ ተጠቃለው በጽ/ቤት ደረጃ እንደሚያቀርቡት ተናግረዋል ፡፡

የግምግማ ፕሮግራሙ በባህልና ቱሪዝም ቢሮ አዳራሽ እንደሚያካሄድ፣ የአንድ ቀን ቆይታ እንደሚኖረውና እንዲሁም ለመድረኩ የሚያስፈልጉ  የቅድመ ዝግጅት ስራዎች መጠናቀቃቸውን ለማወቅ ተችሏል፡፡

                                                                  

                                                                                                                  የኮ/ጉ/ደ/የስራ ሂደት

Press Release Press Release
Minimize Maximize

 የአዲስ አበባ ከተማ  ስራ አስኪያጅ ጽ/ቤት በ6ወር እቅድ የስራ አፈፃፀም ውስጥ የላቀ ውጤት ያስመዘገቡ የስራ ሂደቶች፣ የስራ ክፍሎችና ፈፃሚዎች በቀጣይ ሚያዚያ 05/2008ዓ.ም እውቅና ሊሰጥ ነው፡፡

እንደሚታወቀው የመስሪያ ቤቱ የግማሽ ዓመት የዕቅድ ስራ አፈፃፀም በየስራ ሂደቱ እና በየስራ ክፍሉ እንዲሁም በፈፃሚ ደረጃ ምን ላይ እንዳለ በተቋሙ ባለው የተቋም ለወጥ አገልግሎት ስታንዳርዳይዜሽን ና ምዘና ዋና የስራ ሂደት ከቁልፍ እና ከአብዬት ተግባራት አኳያ በደረጃ የመለየት ስራ ተሰርቷል፡፡ ስለሆነም ይህንን  መሰረት በማድረግ  የላቀ አፈፃፀም ያስመዘገቡ የስራ ሂደቶች፣የስራ ክፍሎችና ፈፃሚዎች የበለጠ ተጠናክረው እንዲቀጥሉና በአፈፃፀም ዝቅተኛ የሆኑት ደግሞ ለተሻለ ስራ እንዲነሳሱና በሰራዊት ቁመና ስራቸውን እነዲያከናውኑ  ታስቦ የተዘጋጀ  የእውቅና ስነስርዓት ነው፡፡ከዚህ ጋር ተያይዞ ለፕሮግራሙ የሚውሉ አስፈላጊ ግብዓቶች ከወዲሁ የተጠናቀቁ መሆኑን ከጽ/ቤቱ ካገኘነው መረጃ ለመረዳት ተችሏል፡፡

 

 

 

 

የኮ/ጉ/ደ/የስራ ሂደት