Mission and Vision Mission and Vision
Minimize Maximize
English (United States) Amharic (Ethiopia) Afar (Ethiopia) Tigrinya (Ethiopia)

የተቋሙ ራዕይ

 

የብልጽግና ማዕከል ከተሞችና ተወዳዳሪ የኮንስትራክሽን ኢንዱስትሪ መገንባት ነው፡፡

 

የተቋሙ ተልዕኮ

 

የባለድርሻ አካላትን በማስተባበርና በማቀናጀት ደረጃውን የጠበቀና ተደራሽ የኮንስትራክሽን ኢንዱስትሪ ውጤቶችና የከተማ የልማትና አገልግሎት በማቅረብ ዜጎችን ተጠቃሚ ማድረግ ነው፡፡

 

የተቋሙ ዓላማ

 

የግል ዘርፉን ጨምሮ የሁሉንም ባለድርሻ አካላትን ተሳትፎ በማሳደግ፣ ተቋማዊ የሥርዓታት ለውጥ በማረጋገጥ፤ ሰፊ የሥራ ዕድል መፍጠር፣ ለአገሪቱ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እድገት መፋጠን ወሳኝ የሆኑ መሰረተ-ልማቶችንና ደረጃውን የጠበቀ አገልግሎት ማስፋፋት፤ በፕላን የሚመሩ ለሥራና ኑሮ ምቹ ለአደጋ የማይበገሩ ከተሞችና ተወዳዳሪና ምርታማ የኮንስትራክሽን ኢንዱስትሪ መገንባት ነው፡፡

 

እሴቶች

 

የተቋም እሴቶች

 

የግልፀኝነት፣ ዕውነተኝነትና ተጠያቂነት አሠራር ማስፈን፣ ውጤታማነትና ለቅልጥፍናን ማረጋገጥ፣ ሁሌም የማያቋርጥ የመማርና የመማማር ሂደትን መከተል፣ ህዝብ ጥቅም ቅድሚያ መስጠት፣ በቡድን የመሥራት ባህል ማጎልበት እና ሁሉንም ሰው እኩል ማየትና የተለያዩ ሃሳቦችን በአግባቡ ማስተናገድ ናቸው፡

 

 

                                               የከተማና መሠረተ ልማት ሚኒስቴር

Print